‹‹ደብረ ዘይት›› የዓብይ ጾም አምስተኛ ሳምንት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ቀኖና መሠረት የዓብይ ጾም አምስተኛ ሳምንት ‹‹ደብረ ዘይት›› በመባል ይከበራል፡፡ ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በደብረዘይት ተራራ ላይ ለደቀ መዛሙርቱ ስለ ዓለም መጨረሻና ዳግም ምጽአቱ በሚገባ አስተምሯል (ማቴ 24 ፥ 1-36)፡፡ በመሆኑም 5ኛው የዓቢይ ጾም ሰንበት የክርስቶስ ነገረ ምጽአት የሚታሰብበትና የሚሰበክበት ዕለት ስለ ሆነ በደብረ ዘይት ተሰይሟል። የደብረ ዘይት ሰንበት ስለምጽአት የተነገረበት ከመሆኑም በላይ በዚህ ዕለት ምጽአት እንደሚሆን ይታመናል፡፡ ጌታችን በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸዉ ወደ እርሱ ቀርበዉ “የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱ ምንድር ነዉ? አሉት።” ለመጀመሪያው ጥያቄ «ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም» (ማቴ.24፥.36) ሲል በአጭሩ ሲመልስ ስለ ሁለተኛው ጥያቄ ማለትም ስለምልክቱ ጉዳይ ግን በሰፊው አስተምሯል። ታዲያ የዓለም መጨረሻ ምልክቱ ምንድን ነው? በመምህር ዶ/ር ዘበነ ለማ የተሰጠውን ትምህርት ከዚህ በታች ባለው ቪዲዮ ይከታተሉ።