በደብራችን ማህደረ ስብሃት ቅድስት ልደታ ለማርያም የተዘጋጀ ታላቅ ኦርቶድክሳዊ ተዋህዶ የወጣቶች ጉባኤ!

ወጣቱንና ዘመኑን የዋጀ ታላቅ ኦርቶድክሳዊ ተዋህዶ የወጣቶች ጉባኤ መምህር ዲያቆን ጎርጎርዮስ ደጀኔን ከሰሜን አሜሪካ ዴንቨር ኮሎራዶ እንዲሁም መምህር ነቅአጥበብ ከፍያልው ከኢትዮጵያ ተጋብዘው በተገኙበት በደብራችን የሚያዘጋጀው ታላቅ የሶስት ቀን የወጣቶች ጉባኤ ከዓርብ ግንቦት 16 እስከ ዕሁድ ግንቦት 18 ቀን 2016 ዓ/ም (f.o.m. 24. t.o.m. 26. mai 2024) ድረስ ይካሄዳል።

መርሃግብሩ ለመጀመርያ ጊዜ በወጣት ኦርቶዶክሳውያን ችግርና መፍትሔ ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የመንፈሳዊ ስልጠናው እና የዕምነት መርሃግብሩን በመላው ኖርዌይ ያሉ ወጣት የቤተ ክርስቲያን ልጆች ይሳተፉበታል።

በጉባኤው ላይ ወጣቶች ሊብራራቸው የሚፈልጉትን መንፈሳዊ ጥያቄዎች በማንሳት ተገቢውን ምላሽ እንዲያገኙና መንፈሳዊ ዕውቀታቸውን እንዲያጎለብቱ ታስቦ የተዘጋጀ ስለሆነ በኦርቶድክሳዊ ተዋህዶ ዕምነት ዙሪያ ወጣቶች ግለጽ ያልሆነላቸውን ጥያቄዎች በማንሳት ነቁ ተሳትፎ እንድያደርጉ የደብሩ የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤ ጥሪውን ያቀርባል።

በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ወጣቶችና ለተጨማሪ መረጃ የደብሩን የሰንበት ት/ቤት ማነጋገር ይቻላል።

Fredag/አርብ
18:00 – 18:30 እንግዶች ቅበላ እና ትውውቅ
18:30 – 19:00 ጉባኤው በአበው ፀሎት ይጀምራል
19:00 – 19:15 መዝሙር
19:15 – 20:00 ትምሕርት በተጋባዥ መምሕር ዲያቆን ጎርጎርዬስ ደጀኔ
20:15 – 20:20 መዝሙር
20:20 – 20:30 ጉባኤው በአበው ፀሎት ይዘጋል
20:30 የእራት መስተንግዶ

Lørdag/ቅዳሜ
07:30 – 08:30 ፀሎት አስተባባሪ
08:30 – 11:30 የቁርስ መስተንግዶ እና ትውውቅ
11:30 – 12:00 ጉባኤው በአበው ፀሎት ይጀምራል
12:00 – 12:15 መዝሙር
12:15 – 13:00 ትምሕርት በተጋባዥ መምሕር ዲያቆን ጎርጎርዬስ ደጀኔ ዲያቆን ጎርጎርዬስ ደጀኔ
13:00 – 13:30 እረፍት
13:30 – 14:30 ጥያቄ እና መልስ መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው
14:30 – 15:00 መዝሙር
15:00 – 17:00 ምሳ
17:00 – 18: 00 ጥያቄ እና መልስ መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው እና ዲያቆን ጎርጎርዬስ ደጀኔ
18:00 – 18:30 መዝሙር
18:30 – 20:30 የእራት መስተንግዶ እና ትውውቅ

Søndag/እሁድ
06:30 – 11:00 ቅዳሴ
11:00 – 12:00 ትምህርት እና መዝሙር መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው እና ዲያቆን ጎርጎርዬስ ደጀኔ
12:00 – 13:00 ምሳ እና እንግዶች ሽኝት