የመንፈሳዊ ትምህርትና ስብከት መርሃ ግብር በመጋቤ ሐዲስ ነቅዓጥበብ ከፍያለው

በስታቫንገር ደብረ ገነት መድሃኔ አለም ወኪዳነ ምህረት ቤ/ክ የተከበረውን የዘንድሮ የጥምቀት በዓል ላይ ከኢትዮጵያ ተጋብዘው የተገኙት መምህር መጋቤ ሐዲስ ነቅዓ ጥበብ ከፍ ያለው በነገው ዕለት ዕሑድ ጥር 19 ቀን 2016 ዓ/ም (søndag 28. januar 2023) በደብራችን ማህደረ ስብሃት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ ተገኝተው ጥልቅ መንፈሳዊ ትምህርታቸን ያስተምሩናል።

በኦስሎና አካባቢው የምትገኙ ምዕመናንና ምዕመናት በተጠቀሰው ቦታና ሰዓት ተገኝታችሁ ከማር የጣፈጠ መንፈሳዊ ትምህርታቸውን እንድትከታተሉ የደብሩ የሰባካ መንፈሳዊ አስተዳደር በማክበር ይጋብዛል።