የዘንድሮ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በድምቀት ተከበረ!

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ!

ቤዛ ኩሉ አለም ዮም ተወልደ / የዓለም ሁሉ ቤዛ ዛሬ ተወለደ!

የሃይማኖት አባቶቻችን «እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ጥበብ ይልቅ በጥፋቱ ወድቆ የነበረውን ዓለም ያዳነበት ጥበቡ ይደንቃል» ይላሉ፡፡

  • እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። የሉቃስ ወንጌል – ምዕራፍ 2:10-11
  • የፍጥረቱቲ መሪ የትሩፋት ጀማሪ ይሆን ዘንድ ሰው ሆነ፡፡ ዮሐ. 13፣14፡፡
  • ሕዝብና አሕዛብን አንድ ሊያደርግ እግዚአብሔር ሰው ሆነ፡፡ ገላ. 3፡28፡፡
  • ሞትን በሞቱ ይሽረው ዘንድ እግዚአብሔር ሰው ሆነ፡፡ 1ቆሮ. 1፡20፡፡
  • በሥጋ ከይሲ ተሰውሮ የመጣውን ዲያብሎስን በመስቀሉ ድል ይነሳው ሥልጣኑንም ይገፍፈው ዘንድ ሰው ሆነ፡፡ ቆላ. 2፡14፡፡
  • ሀብታም ሲሆን፣ እኛ በእርሱ ድህነት ባለጠጎች እንሆን ዘንድ ስለእኛ ድሀ ሆነ፡፡ 2ቆሮ. 8፡9፡፡
  • አዳምን ወደ ክብር ቦታው ለመመለስ እርሱ ማደሪያ ስፍራ አጥቶ በግርግም /በከብቶች በረት – በበጎች ጉረኖ/ ተወለደ፡፡ ሉቃስ 2፡7፡፡

የዘንድሮን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ከዋዜማው ከቅዳሜ ታህሳስ 27 ቀን 2016 ዓ/ም (06. januar 2024) ከምሽቱ 19:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ዕሑድ ጠዋት ድረስ በማህሌት፣ በዝማሬ፣ በስብከት፣ በቅዳሴና ሌሎች በተለያዩ መርሃ ግብሮች በታላቅ ድምቀት ተክብሮ ዋለ፡፡