ሰሞነ ህማማት

ከሆሳዕና ጀምሮ እስከ ትንሳኤ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ የዘንድሮው ሰሞነ ህማማት ክሰኞ ሚያዚያ 21 ቀን 2016 ዓ/ም (29. april 2024) ይጀምራል።

ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ሲል የተቀበለውን መከራና ፍዳ በማስታወስ ክርስቲያኖች የክርስቶስን ውለታ እያሰቡ እጅግ የሚያዝኑበት፣ የሚያለቅሱበት፣ የሚሰግዱበት፣ ከሌላው ቀናትና ጊዚያት በተለየ መልኩ አምላካቸውን የሚማፀኑበት፣ ጥዋት ማታ አምላካቸውን ደጅ የሚጠኑበት፣ ሀጢያታቸውን በቤተክርስቲያን አደባባይ ለካህኑ የሚናዘዙበት ሳምንት ነው፡፡ በዚህ ሳምንት ውስጥ ታላላቅ በዓላት ማለትም ጸሎተ ሐሙስ (ህጽበት እግር)፣ ስቅለትና ቀዳም ሥዑር ይገኙበታል። ስለሆነም ምዕመናንና ምዕመናት በቤተ ክርስቲያናችን በወጣው ፕሮግራም መሰረት ከጠዋቱ 07:00 ሰዓት ጀምሮ ቤተ ከርስቲያኑ ለመንፈሳዊ አገልግሎት ክፍት ሆኖ ይውላል። ምዕመናንና ምዕመናት በቦታው ተግኝታችሁ የአገልግሎቱና የበረከቱ ተካፋዮች እንድትሆኑ የደብሩ ሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባዔ ያስታውቃል።

ይህ ሰሞነ ህማማት ከአምላካችን ጋር የምንገናኝበት የንስሀ፣ የጾምና የፀሎት ጊዜ ይሁንልን አሜን!!!