“ምኩራብ” የዐቢይ ጾም 3ኛ ሳምንት

የዐቢይ ጾም 3ኛ ሳምንት ስያሜ “ምኩራብ” ይባላል። “ምኩራብ” ማለትም ቀጥተኛ ፍችው ኮረብታ፣ ተራራ የሚያኸል ታላቅ ሕንጻ ማለት ሲሆን ከዚህም የተነሣ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ምኩራብ በመባል ይታወቃል። ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎችን ለማስወጣቱ፣ ቤተ መቅደሱን ለማስከበሩ መታሰቢያ ሆኖ የተሰጠ ስያሜ ነው።
“ኢየሱስም ወደ መቅደስ ገባና በመቅደስ የሚሸጡትንና የሚገዙትን ሁሉ አወጣ፥ የገንዘብ ለዋጮችንም ገበታዎች የርግብ ሻጮችንም ወንበሮች ገለበጠና። “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፎአል፥ እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት” አላቸው።” ማቴ 21፡12-13

የዕለቱ ምስባክ: “የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና፥ የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆአልና። ነፍሴን በጾም አስመረርሁአት፥ ለስድብም ሆነብኝ።” መዝሙረ ዳዊት – ምዕራፍ 69:9-10

ይህንን በተመለከተ በዶ/ር ቀሲስ ዘበነ ለማ ከዚህ በፊት የተሰጠውን ትምህርት ከዚህ በታች በተቀመጠው ቪዲዮ ያድምጡ።