መርሐ ግብር

ዘወትር ዕሑድ ከጠዋቱ 7 ሰአት ጀምሮ የቅዳሴ ሥነ ሥርዓት፣ የስብከትና የመዝሙር መርሃ ግብር በቤተ ክርሥቲያናችን (Caspar Storms vei 12, 0664 Oslo) ይካሄዳል፡፡ ምዕመናንና ምዕመናት በቦታውና በሰዓቱ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድትሆኑ የደብሩ የሰበካ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባዔ በማክበር ይጋብዛል፡፡

እንዲሁም ዘወትር ዕሑድ ከቅዳሴ በኋላ የሰንበት ት/ቤ ለህጻናት የቋንቋ፣ የመጽሃፍ ቅዱስና የመዝሙር ትምህርት በቤተ ክርሥቲያኑ ውስጥ ስለሚሰጥ ወላጆች ልጆቻችሁን በማምጣት እንድታሳትፉ የሰንበት ትምህርት ቤቱ በማክበር ይጠይቃል፡፡