እንኳን ለሊቀ መላኩ ቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን !

ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ዑርኤል በመብረቅ በነጐድጓድ የተሾመ ነው። መጽሐፈ ሄኖክ 6:2

ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ በመሆኑም ሐምሌ 22 ቀን ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበትን ዕለት የሚከበርበትና የሚዘከርበት ዕለት ነው። ጥር 22 በዓለ ሲመቱ ነው። መጋቢት 27 የጌታችንን ክቡር የሆነ ወርቀ ደሙን ለዓለም የረጨበት ዕለት ነው።

“ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ” መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል 2፡1

የቅዱስ ዑራኤል በረከት በሁላችንም ላይ ይደር!! አሜን!