እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን !!!

በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሥጋ መከራ እንደታደጋቸው፣ ከፈላ የብረት ጋን እንዳወጣቸውና ከሞት አደጋ እንደታደጋቸው የሚታሰብበት ዕለት ነው። ታሪኩም በመጽሐፈ ስንክሳር፣ በድርሳነ ገብርኤል እና በገድለ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ተመዝግቦ ይገኛል።

የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት፣ የሰማዕታቱ የቅዱስ ቂርቆስና ቅዱስ ኢየሉጣ የገድላቸው በረከት ይደርብን!
ሰማዕቱ ቅዱስ ቂርቆስን እና እናቱ ቅድስት እየሉጣን ከፍቱን እሳት ከፈላው ውኃ ያዳንካቸው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እኛ ልጆችህን አድነን ለሀገራችን ሰላም ለህዝባችን አስተዋይ ልቦናን አድልልን!

የእግዚአብሔር ቸርነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን!