እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

የደብረ ታቦር (የቡሄ) በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሀዶ ቤ/ክ ቀኖና መሰረት ከዘጠኙ አብይ በዓላት ውስጥ አንዱ ሲሆን የሚከበረውም ጌታ እየሱስ ክርስቶስ በማስተማር በነበረበት ጊዜ በደብረ ታቦር ላይ ብርሃነ መለኮቱን ክብረ መንግስቱን የገለፀበት ዕለትን ለማስታወስ ነው። ይህ በዐል በየአመቱ ነሃሴ ፲፫ (13) ቀን ይከበራል።
“ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ማቴ 17:1-3