እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በስለም አደረሳችሁ፣ አደረሰን አሜን!

ጾመ ፍልሰታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፷፬ ዓመት በዚች ምድር ኖራ እንደ አንድ ልጇ መሞቷን፣ መነሳቷንና ማረጓን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት የጾሙት ጾም ነው። ጾሙን ነሐሴ ፩ ቀን ጀምረው በነሐሴ አሥራ አራት ቀን ጌታችን እመቤታችንን አምጠቶ እንድትገለጥላቸው አደረገ፤ ቀበሯትም፡፡ በነሐሴ አሥራ ስድስት ቀንም እርገቷን አከበሩ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን የእመቤታችንን በረከት ለማግኘት ከነሐሴ ፩ ቀን እስከ ነሐሴ ፲፮ ቀን ጾመ ፍልሰታ በመባል ትጾማለች፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዋጅ ከደነገገቻቸው ሰባቱ አጽዋማትም አንዱ ነው። በዚህ ወቅት ምእመናንና ምዕመናት በፆም በጸሎት ተወስነው የልጇን ቸርነት የድንግልን አማላጅነት ይማጸናሉ፡፡ ሙሉ ታሪኩን ከዚህ በታች በሚገኘው የአውዲዮ ሊንክ በመጫን አዳምጡ!

ጾሙን ጾመ ደህነት፣ ጾመ በረከት፣ በንሰሀ ተመልሰን ሥጋውና ደሙን ተቀብለን ከእመቤታችን በረከት አግኝተን መንግስቱን ለመወረስ የምንዘጋጅበት ያድርግልን!