የሰሙነ ሕማማት አምስተኛው ቀን ዕለተ ዓርብ”ስቅለት”

ዕለተ ዓርብ እኛ የሰው ልጆች በኃጢአት ቁራኝነት እንኖርበት የነበረው የጨለማ ሕይወት ያከተመባትና ፍጹም ድኅነት ያገኘንባት ታላቅ ዕለት ናት፡፡ ዕለቱም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ሁሉ መድኃኒት ለአዳምና ለልጆቹ ሲል በመልእልተ መስቀል በቀራንዮ አደባባይ ተሰቅሎ መዋሉን የምናስብበት ታላቅ ቀን ነው፡፡ ማቴ.27-35-75፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ “አውቀውስ ቢሆን የክብርን ጌታ ባልሰቀሉት»(1ቆሮ.1-18)” እንዳለ ይህ ዕለት የአይሁድ ካህናት ያለበደል ያለጥፋት ንጹሕና ጻድቅ የሆነውን ጌታ የሰቀሉበት ዕለት ነው፡፡ ሕዝበ ክርስቲያን በዕለተ ዓርብ ቀኑን በሙሉ በቤ/ክርስቲያን በመሰባሰብ የክርስቶስን ሕማሙን፣ ስቃዩን፣ ስቅለቱንና ሞቱን በስግደትና በጸሎት ይዘክራሉ፡፡
በዚሁ መሠረት ቤተ ክርስቲያናችን ለዚሁ አገልግሎት አርብ 03/05-2024 ከጠዋቱ 07:00 ሰዓት ጀምሮ ክፍት ሆኖ ይውላል።
ምዕመናንና ምዕመናት በተጠቀሰው ቦታና ሰዓት በመገኘት የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ የደብሩ መንፈሳዊ አስተዳደር ይጋብዛል።