ዕለተ ቀዳሚት ሥዑር

በዚህች ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከርሰ መቃብር ዐርፎ የዋለባት ዕለት በመሆኗ ‹‹ቀዳሚት ሥዑር›› ትሰኛለች፡፡ ‹‹ቀዳሚት ሥዑር›› የተባለችበት ምክንያትም በዓመት አንድ ቀን ስለ ምትጾም ነው፡፡ ዕለቱን በተመለከተ ከዚህ በፊት በመምህር ዘበነ ለማ የተሰጠውን ትምህርት ከዚህ በታች የተቀመጠውን ትምህርት ያድምጡ።

የዘንድሮን የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ በዋዜማው ቅዳሜ ሚያዚያ 26 ቀን 2016 ዓ/ም (04. mai 2024) ከምሽቱ 20:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 0300 ሰዓት ድረስ የማህሌት፣ የዝማሬና የቅዳሴ ሥነ ሥርዓት ይካሄዳል፡፡ ለትራንስፖርት እንዲያመች ቤ/ክርስቲያኑ እስክ ጠዋቱ 06:00 ሰዓት ድረስ ከፍት ሆኖ ይሆናል።

በኦስሎና አካባቢው የምትገኙ ምዕመናንና ምዕመናት በተጠቀሰው ቦታና ሰዓት በመገኘት የበዓሉና የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ የደብሩ መንፈሳዊ አስተዳደር ይጋብዛል፡፡