ግንቦት 1 ቀን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል

የዘንድሮ 2016 ዓ/ም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በቤተ ክርስቲያናችን በዕለተ ቀኗ በመጪው ሐሙስ ግንቦት 1 ቀን ከኢትዮጵያ፣ ካውሮፓና ከኖርዌይ የተጋበዙ መምህራን፣ ቀሳውስትና መዘምራን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት በማህሌት፣ በመዝሙር፣ በቅዳሴና ታቦተ ንግስ ይከበራል።

ቤተ ክርስቲያኑ ከዋዜማው ረቡዕ ሚያዚያ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ከምሽቱ 20:00 ሰዓት ጀምሮ ከኢትዮጵያ በሚመጡት መምህር መጋቤ ሐዲስ ነቅዓጥበብ ከፍያለው በትምህርትና ስብከተ ወንጌል ተጀምሮ የማህሌት፣ የመዝሙር፣ የቅዳሴና ታቦተ ንግስ መርሃ ግብሩ በተከታታይ እስከ ሚቀጥለው ግንቦት 1 ቀን ድረስ ይከናወናል።

በኦስሎና አካባቢው የምትገኙ ምዕመናንና ምዕመናት በተጠቀሰው ቦታና ሰዓት ተገኝታችሁ የበዓሉና የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ የደብሩ የሰባካ መንፈሳዊ አስተዳደር በማክበር ይጋብዛል።

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት በተመለከተ “ልደታ ለማርያም ከዕሴይ ስር በትር ትወጣለች” በሚል አስተምሮ ዘተዋህዶ ገጽ ላይ የተቀመጠውን ትምህርት እዚህ ላይ በመጫን ይመልከቱ።