የዐብይ ጾም ሁለተኛው ሰንበት “ቅድስት”

የዐቢይ ጾም ሁለተኛው ሰንበት ኢትዮያዊው የዜማ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ እንደሰየመው “ቅድሰት” ይባላል። ቅድስት ማለት ልዩ፣ ጽኑዕ፣ ክቡር ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን በባሕርዩ ቅዱስ ነው፡፡ ስለሆነም በመልኩና በምሳሌው አክብሮ የፈጠረንን እኛም ቅዱሳን እንድንሆን ይፈለጋል፡፡ “ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ” 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1:15-16፡፡ ከዚህ ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፣ ይሰበካል። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱንና ሳምንቱን ስለ ቅድስና ታስተምራለች፡፡ ይህንን በተመለከተ በዶ/ር ቀሲስ ዘበነ ለማ ከዚህ በፊት የተሰጠውን ትምህርት ከዚህ በታች ያለውን ቪዲዮ ይመልከቱ።

የዕለቱ ምስባክ “እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ። ምስጋናና ውበት በፊቱ፥ ቅዱስነትና ግርማ በመቅደሱ ውስጥ ናቸው።” መዝ 96:5-6

የዕለቱ ወንጌል “ስትጦሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።” የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 6: 16