ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ በነገው ዕለት በደብራችን ተገኝተው በኖርዌይ ተወልደው፣ ተምረው ደቀ መዛሙርት ለሚሆኑ ልጆቻችን ሥልጣነ ክህነትን ይሰጣሉ።

አባታችን ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ በኢ.ኦ.ተ.ቤ. የምስራቅ ጎጃም እንዲሁም የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ በሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ኤልያስ በጎ ፈቃድ በደብራችን በማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው በነገው ዕለት የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ/ም (18. februar 2024) በኖርዌይ ሃገር ተወልደው፣ ተምረው ለዲቁና ለደረሱ ደቀ መዛሙርት ለሚሆኑ ልጆቻችን ሥልጣነ ክህነትን ይሰጣሉ።

በኦስሎ እና አካባቢው የምትገኙ ምዕመናን እና ምዕመናት በተጠቀሰው ቀን እና ቦታ ከጠዋቱ 06:00 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት መርሃ ግብሩን እንድትሳተፉ እንዲሁም ከብፁዕነታቸው ቡራኬና ቃለ ምዕዳን ትቀበሉ ዘንድ የደብሩ ሰበካ ጉባዔ ጽ/ቤት መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል።