“ገብር ሔር” የዐቢይ ጾም ስድስተኛው ሳምንት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስያሜ መሠረት የዐቢይ ጾም ስድስተኛው እሑድ ወይም ሳምንት ገብር ሔር ይባላል፡፡ ገብር ሔር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምሳሌ መስሎ ካስተማራቸው ትምህርቶች መካከል አንዱ የሆነው ይህ ታልቅ ትምህርት በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 25፥14-25 እንደተገለጸው ቤተ ክርስቲያን በዚህ ሳምንት የተሰጣቸውን ጸጋ አውቀው፣ ተርድተውና ተቀብለው በታማኝነት ኃለፊነታቸውን የተወጡ መልካም አገልጋዮች በጌታቸው ፊት “…አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ…” በመባል መወደሳቸውና መሸለማቸው ይነገራል፣ ይወሳል፣ ይሰበካል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ የተሰጠውን ጸጋ ሳያውቅና ሳይረዳ ቸል ብሎ ኃላፊነቱን ያልተወጣ እኩይ ሎሌ በጌታው መወቀሱና መቀጣቱ የሚነገርበት፣ የሚወሳበትና የሚሰበክበት ሳምንት ነው፡፡ ዕለቱን በተመለከተ በመምህር ዶ/ር ዘበነ ለማ ከዚህ በፊት የተሰጠውን ትምህርት ከዚህ በታች ባለው ቪዲዮ ይከታተሉ።