የቤተ ክርስቲያናችን አባል ይሁኑ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የኦስሎ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ አባል ለመሆን ይመዘገቡ ዘንድ በታላቅ መንፈሳዊ አክብሮት ጥሪውን ያቀርባል።

በአባልነት የሚገኝ ጥቅም

ማንኛውም ሰው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ከተጠመቀ በኃላ ክርስቲያን ይሆናል ክርስቲያን የሚሆነው በክርስቶስ በማመን ሲጠመቅ ነው። ከጥምቀትም በኃላ የሚከተሉትን ያገኛል

  • እግዚአብሔር በሚሰጠው የልጅነት ጸጋ የመንግሥቱ ወራሽ ይሆናል፤
  • የበደልን እና የኃጢያትን ሥርየት ይቀበላል፤
  • በቤቱ ልጅና ወራሽ በመሆን ከእርሱ በሆነ ጸጋ የመንፈሳዊ በረከት ሁሉ ተካፋይ ይሆናል፡

በመሆኑም ጥንታዊና ታሪካዊ በሆነች በአንዲት የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእምነት ጥላ ሥር በመሆን በአጥቢያችን ከምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ጋር ህብረት ሲኖረው የሚያገኘው የማይቋርጥ ጸጋ ነው። ስለዚህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኖርዌይ ኦስሎ የማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ ከላይ ከተገለጸው መንፈሳዊ በረከት በተጨማሪ የሚከተለውን መንፈሳዊ አገልግሎት ትሰጣለች፦

  • ጥምቀት፤ ተክሊል እና ጸሎተ ፍታት
  • የካህናት ምክር
  • ለህጻናትና ለወጣቶች ታሪክን፣ ባህልን፣ ቋንቋንና ክርስቲያናዊ ግብረገብነትን ማስተማር
  • የአባልነት ማስረጃ ለሚያስፈልጋቸውና በቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደር ውስጥ መሳተፍ፤ መመረጥና መመረጥ፤

በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም አባል ለመሆን ይመዝገቡ ዘንድ በታላቅ መንፈሳዊ አክብሮት እንጠይቃለን። ለአሰራር ቅልጥፍና በዚሁ ድኅረ ገጽ የሚገኘውን የአባልነት ፎርም በመሙላት ቅጹን ሞልተው በሜይል አድራሻቸን አባሪ በማድረግ ቢልኩልን በቀላሉ መመዝገብ እንችላለን፡፡ በማንኛው የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎት ጥያቄ ካልዎት መልስ እንሰጣለን።

የመመዝገቢያ ቅጹን ከዚህ ያውርዱ (PDF)