ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

የዘንድሮ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በድምቀት ተከበረ!

ቤዛ ኩሉ አለም ዮም ተወልደ / የዓለም ሁሉ ቤዛ ዛሬ ተወለደ
የዘንድሮን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ከዋዜማው ከቅዳሜ ታህሳስ 27 ቀን 2016 ዓ/ም (06. januar 2024) ከምሽቱ 19:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ዕሑድ ጠዋት ድረስ በማህሌት፣ በዝማሬ፣ በስብከት፣ በቅዳሴና ሌሎች በተለያዩ መርሃ ግብሮች በታላቅ ድምቀት ተክብሮ ዋለ፡፡ 

የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል!

“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” መዝ. 33፡7
የዘንድሮው የታህሳስ ወር የሊቀ መላዕክት የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቤተ ክርሥቲያናችን ዓርብ ታህሳስ 19 ቀን (29. desember 2023) ከጠዋቱ 07:00 ሰዓት ጀምሮ በማህሌት፣ በዝማሬ፣ በስብከተ ወንጌል፣ በታቦተ ንግስ እንዲሁም ከቀኑ 12 ሰዓት ጀምሮ በቅዳሴ በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል።

አዲስ ድረገጽ ተለቀቀ

የቤተክርስቲያናችን ድረገጽ በአዲስ መልኩ ተሠርቶ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ

በፌስቡክ ያግኙን

አባልነት

በአባልነት ለመመዝገብ የምትፈልጉ የአባልነት ፎርምና ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት

የገንዘብ አስተዋጻኦ

የባንክ ሂሳብ ቁጥር፡ 1503 622 909

111030

በቋሚነት

በቋሚነት በየወሩ በቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም በቪፕስ ለመክፈል

Minside

ስለ እኛ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ የኦስሎ ማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የማህደረ ስብሃት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ በጥቂት ግለሰቦች አነሳሽነትና በእግዚአብሔር ፈቃድ መጋቢት 6 ቀን 2007 ዓ/ም ተመሠረተ፡፡ በወቅቱ የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹእ አቡነ እንጦስ በቦታው ተገኝተው ቤተ ክርስቲያኑን ባርከውና ቀድሰው መሠረት ከመጣላቸውም በላይ በቀጣይነት ከአንድ ዓመት በኋላ የሊቀ መላኩን የቅዱስ ገብርኤል ጽላት በማስመጣት ለቤ/ክርስቲያኑ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ሲመሰረት 19 ምዕመናንና ምዕመናት በአባልነት ተመዝግበው የነበሩት ሲሆን በአሁኑ ወቅት የአባላት ቁጥር ከ200 በላይ ሆኗል፡፡ ቋሚ ቤ/ክ ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ቢሆንም ለጊዜው በኪራይ ቀደም ሲል በካምፐን ሜኒሄትስ ሁስና በካምፐን ሺርከ አሁን ደግሞ በCaspar Storms vei 12, 0664 Oslo, የሰንበት ቅዳሴ፣ የሰንበት ት/ቤትና እንዲሁም የበዓላት መርሃ ግብር ሳይታጎሉ ቤተ ክርስቲያኑ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ ያልተቋረጠ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።

ፎቶ፦ ብጹዕ አቡነ እንጦስ ቤተክርስቲያናችህንን ባርከው አገልግሎት ሲያስጀምሩ

ያግኙን

  • Tel: +47 462 21 386
  • Epost: post@lidetalemariam.no
  • Postadresse: Jerikoveiene 93A, 1052 Oslo
  • Besøkadresse: Caspar Storms vei 12, 0664 Oslo
  • Org.nr. 915 237 118
  • Bank Account: 1503 622 9095
  • Vipps: 111030