ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

ፆመ ፅጌ – ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፭

በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም በተወለደ ጊዜ ንጉሥ ሄሮድስ ሥልጣኔን ይቀማኛል በሚል ቅናት ተነሣሥቶ እርሱን ለማስገደል አሰበ፡፡ ያንጊዜም ጌታችን በተአምራት መዳን ሲቻለው የትዕግሥት፣ የትሕትና አምላክ ነውና በለበሰው ሥጋ በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ጀርባ ታዝሎ በመልአኩ ተራዳኢነት፣ በአረጋዊው ዮሴፍ ጠባቂነትና በሰሎሜ ድጋፍ ከገሊላ ወደ ግብፅ ተሰዶ ሄሮድስ እስኪሞት ድረስ ቆይቷል፡፡ ሄሮድስም ጌታችንን ያገኘው መስሎት በቤተ ልሔምና በአውራጃዋ የሚገኙ ሀለት ዓመት ከዚያ በታች የሆኑ አንድ መቶ ዐርባ አራት ሺሕ ሕፃናትን በግፍ አስፈጅቷል፡፡
በተአምረ ማርያምና በማኅሌተ ጽጌ ተጽፎ እንደሚገኘው ጌታችን በግብጽ ምድር በስደት ሳለ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን አድርጓል፡፡ ከእነዚህ መካከልም ውሃ በጠማቸው ጊዜ ውሃ እያፈለቀ ማጠጣቱና ይህንን ውሃ ክፉዎች እንዳይጠጡት መራራ ማድረጉ፤ ለችግረኞችና ለበሽተኞች ግን ጣፋጭ መጠጥና ፈዋሽ ጠበል ማድረጉ፤ ‹‹የሄሮድስ ጭፍሮች ደርሰው ልጅሽን ሊገድሉብሽ ነው›› ብሎ የዮሴፍ ልጅ ዮሳ እመቤታችንን በማስደንገጡ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ድንጋይ ሆኖ እንዲቆይ ማድረጉ፤ መንገድ ላይ የተራዳቸው ሽፍታ ሰይፉ በተሰበረች ጊዜ እንደ ቀድሞው ደኅና እንድትሆን ማድረጉ፤ እንደዚሁም የግብጽ ጣዖታትን ቀጥቅጦ ማጥፋቱ ተጠቃሾች ናቸው፡፡

ደመራ እና ብርሃነ መስቀሉ

እንኳን ለደመራ እና ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ።

እያልን የደመራን በዓል ዐርብ መስከረም 16 (september 26) ከ 16 ስዓት ጀምሮ በድምቀት እናከበራልን። የበረከቱ ተካፋይ እንድትሆኑ በእግዚአብሔር ስም ጥሪ እናቀርባለን።
አድራሻ – Lille-Wembley, Haugerudveien 79, Oslo

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል

ጸሎት

ለወደፊቱ ይህንን የመሳሰሉ አንዳንድ አጫጭር ጥቅሶችን እና ትምህርቶችን ፖሰት ሰለምናደርግ እንድትከታተሉ በትህትና እናሳስባለን። ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር አድርጉ።

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

በዓሉን በደብራችን በማኀደረ ስብሐት አርብ ግንቦት ፩ (May 9) ከጠዋቱ 06:00 – 12:00 ሰዓት ሥርዓተ ቅዳሴ እና እለቱን የተመለከተ ትምህርት እንዲሁም ዝማሬ እና የጸበል ጻዲቅ መርኃ ግብር ይኖራል።

ቅዳሜ ግንቦት ፪ (May 10) ከ15:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ እሁድ ግንቦት ፫ (May 11) በታላቅ መንፈሳዊ ሥርዓት በመዝሙር፣ በትምህርት፣ በማህሌት እና በቅዳሴ በ Vålerenga kirke ይከበራል። ለበዓሉ አባቶች ካህናት እና መምህራነ ወንጌል ከኢትዮጵያና ከአካባቢው ሀገራት ተጋብዘዋል።

Vålerenga kirke Hjaltlandsgata 3, 0658 Oslo

ኒቆዲሞስ (የዐብይ ጾም ፯ኛ ሳምንት)

ኒቆዲሞስ ቃሉ የግሪክ ሲሆን ድል ማድረግን ወይም አሸናፊነትን ያመለክታል፡:

ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ፥ ከአይሁድ አለቆችና መምህራን አንዱ ነው። በወንጌለ ዮሐንስ ምዕራፍ ሦስት ከፈሪሳውያንወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ የተባለ አንድ ሰውእንደነበረና እርሱም በሌሊት ወደ ጌታችን መጥቶ እንደተማረተጠቅሷል። (ዮሐ ፩–፪)በአይሁድ አለቆች ፊትም ”ሕጋችን አስቀድሞ ሳይሰማየሠራውንም ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን?” በማለት ስለ ክርስቶስ የተናገረ እሱ ነው። እነርሱ ግን በክርስቶስ ያመኑበት ኦሪትን የማያዉቁ ስሑታን እንደሆኑ ያስቡ ስለ ነበር ”አንተም ደግሞ ከገሊላ ነህን? ከገሊላ ነቢይ እንደማይነሳ መርምርና እይ“ አሉት እንጂ አልተቀበሉትም። ዮሐ፯፥፵፰–፶፪።

የዘንድሮ 2017 ዓ/ም ጾመ ነነዌ!

የዘንድሮ የነነዌ ጾም ከነገ የካቲት 03 ቀን 2017 (fra 10. febryar 2025) ጀምሮ ለሶስት ቀናት ይጾማል። ሦስት ቀናት የሚጾመው ይህ ጾም የነነዌን ሕዝብ ከጥፋት መመለስ፣ የእግዚአብሔርን ምሕረት እንዲሁም የነቢዩ ዮናስን የዋህነት ያስረዳናል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የዘንድሮን የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ አስመልክተው መግለጫ አስተላልፈዋል፡፡

የዘንድሮ 2017 ዓ/ም የጥምቀት በዓል ቅዳሜ ጥር 10 እና ዕሑድ ጥር 11 ቀን 2017 ዓ/ም (18. og 19. januar 2025) በበርገን መንበረ ልዑል ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ትክብሮ ይውላል!

የዘንድሮ 2017 ዓ/ም የጥምቀት በዓል እንደወትሮው በኖርዌይ ውስጥ በሚገኙ ትላልቅ አድባራት ማለትም
– የበርገን መንበረ ልዑል ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ
– የስታቫንገር ደብረ ገነት መድሃኔ አለም ወኪዳነ ምህረት ቤ/ክ
– የኦስሎ ማህደረስብሃት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ
– የክርስቲያንሳንድ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ
-የትሮንድሐይም ምስራቀ ጸሃይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ታቦታት በጋራ በተሳተፉበት በበርገን መንበረ ልዑል ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ አዘጋጅነት በበርገን ከተማ (Vilhelm Bjerknes vei 24, 5081 Bergen) ቅዳሜና ዕሑድ ጥር 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ/ም (18. og 19. januar 2025) በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ይውላል።

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ቤዛ ኩሉ አለም ዮም ተወልደ / የዓለም ሁሉ ቤዛ ዛሬ ተወለደ!
የዘንድሮን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ ሰኞ ታህሳስ 28 ቀን 2024 ዓ/ም ከምሽቱ 20:00 ሰዓት ጀምሮ በማህሌት፣ በዝማሬ፣ በቅዳሴና ሌሎች የተለያዩ መርሃ ግብሮች በቤተ ክርስቲያናችን ተከብሮ ይውላል።
በኦስሎና አካባቢው የምትገኙ ምዕመናንና ምዕመናት በተጠቀሰው ቦታና ሰዓት ተገኝታችሁ በዓሉን በጋራ እንድናከብር የደብሩ መንፈሳዊ አስተዳደር ጉባኤ በማክበር ይጋብዛል!

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” መዝ. 33፡7
የዘንድሮው የታህሳስ ወር የሊቀ መላዕክት የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቤተ ክርስቲያናችን ቅዳሜ ታህሳስ 19 ቀን (28. desember 2024) ከዋዜማው ከሌሊቱ 01፡00 ሰዓት ጀምሮ በማህሌት፣ በዝማሬ፣ በስብከተ ወንጌል፣ በቅዳሴና በታቦተ ንግስ በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ይውላል። በዕለቱም የቤተ ክርስቲያኒቱ የ5 ዓመት (2025 – 2030) መሪ ዕቀድ ለምዕመናንና ምዕመናት ቀርቦ ይጸድቃል።
በኦስሎና አካባቢው የምትገኙ ምዕመናንና ምዕመናት በተጠቀሰው ቦታና ሰዓት ተገኝታችሁ በዓሉን በድምቀት በማክበር የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ የደብሩ የሰባካ መንፈሳዊ አስተዳደር በማክበር ይጋብዛል።

በፌስቡክ ያግኙን

አባልነት

በአባልነት ለመመዝገብ የምትፈልጉ የአባልነት ፎርምና ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት

የገንዘብ አስተዋጻኦ

የባንክ ሂሳብ ቁጥር፡ 1503 622 909

111030

በቋሚነት

በቋሚነት በየወሩ በቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም በቪፕስ ለመክፈል

Minside

ስለ እኛ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ የኦስሎ ማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የማህደረ ስብሃት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ በጥቂት ግለሰቦች አነሳሽነትና በእግዚአብሔር ፈቃድ መጋቢት 6 ቀን 2007 ዓ/ም ተመሠረተ፡፡ በወቅቱ የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹእ አቡነ እንጦስ በቦታው ተገኝተው ቤተ ክርስቲያኑን ባርከውና ቀድሰው መሠረት ከመጣላቸውም በላይ በቀጣይነት ከአንድ ዓመት በኋላ የሊቀ መላኩን የቅዱስ ገብርኤል ጽላት በማስመጣት ለቤ/ክርስቲያኑ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ሲመሰረት 19 ምዕመናንና ምዕመናት በአባልነት ተመዝግበው የነበሩት ሲሆን በአሁኑ ወቅት የአባላት ቁጥር ከ200 በላይ ሆኗል፡፡ ቋሚ ቤ/ክ ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ቢሆንም ለጊዜው በኪራይ ቀደም ሲል በካምፐን ሜኒሄትስ ሁስና በካምፐን ሺርከ አሁን ደግሞ በCaspar Storms vei 12, 0664 Oslo, የሰንበት ቅዳሴ፣ የሰንበት ት/ቤትና እንዲሁም የበዓላት መርሃ ግብር ሳይታጎሉ ቤተ ክርስቲያኑ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ ያልተቋረጠ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።

ፎቶ፦ ብጹዕ አቡነ እንጦስ ቤተክርስቲያናችህንን ባርከው አገልግሎት ሲያስጀምሩ

ያግኙን

  • Tel: +47 462 21 386
  • Epost: post@lidetalemariam.no
  • Postadresse: Jerikoveiene 93A, 1052 Oslo
  • Besøkadresse: Caspar Storms vei 12, 0664 Oslo
  • Org.nr. 915 237 118
  • Bank Account: 1503 622 9095
  • Vipps: 111030