“መጻጉ” የዐቢይ ጾም 4ኛ ሳምንት
የዐቢይ ፆም አራተኛው ሳምንት መጻጉዕ ይባላል፡፡ ይህ ዕለት አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያንን መፈወሱ የሚዘከርበት ሳምንት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንም በዚህ ዕለት ስለ ጌታችነ ገቢረ ተዓምራትና ስለ ድውያን ፈውስ በሰፊው ታስተምራለች። መጻጉ በቤተ ሳይዳ የጸበል መጠመቂያ ቦታ ለ38 ዓመት የአልጋ ቁራኛ ሆኖ ለመዳን በተስፋ ሲጠባበቅ የነበረ ሰው ነበር፡፡ ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ብዙ ዘመን ተኝቶ እንደኖረ አውቆ «ልትድን ትወዳለህን?» አለው፡፡ እርሱም መጠቂያው ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም በማለት መልስ ሰጠ፡፡ ጌታችን የሁሉም መድኃኒት በመሆኑ ወዲያው ‹‹ተነስተህ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ» ሲለው ድኖ አልጋውን ተሸክሞ ሄደ። የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 5: 1-15 ። ይህንን በተመለከተ በዶ/ር ቀሲስ ዘበነ ለማ ከዚህ በፊት የተሰጠውን ትምህርት ከዚህ በታች በተቀመጠው ቪዲዮ ያድምጡ።



የዐቢይ ጾም ሁለተኛው ሰንበት ኢትዮያዊው የዜማ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ እንደሰየመው “ቅድሰት” ይባላል። ቅድስት ማለት ልዩ፣ ጽኑዕ፣ ክቡር ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን በባሕርዩ ቅዱስ ነው፡፡ ስለሆነም በመልኩና በምሳሌው አክብሮ የፈጠረንን እኛም ቅዱሳን እንድንሆን ይፈለጋል፡፡ “ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ” 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1:15-16፡፡ ከዚህ ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፣ ይሰበካል። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱንና ሳምንቱን ስለ ቅድስና ታስተምራለች፡፡ ይህንን በተመለከተ በዶ/ር ቀሲስ ዘበነ ለማ ከዚህ በፊት የተሰጠውን ትምህርት ከዚህ በታች ያለውን ቪዲዮ ይመልከቱ።